ዜና/ፓለቲካ
ደመቀ መኮንን ትናንት በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ላጎደልኩት ነገር ሁሉ ይቅርታ እጠይቃለሁ ብለዋል።
ትናንት 'ለት ከገዢው ብልጽግና ፓርቲ የምክትል ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በአመራር ዘመናቸው -አጉድየዋለሁ- ላሉት ነገር በይፋ ይቅርታ ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ የሚስተዋለውን የሀገረ መንግስት ግንባታ ፈተና ለመሻገር ሕገ መንግስትን ከማሻሻል ጀምሮ ሌሎች ስብራቶችን ማረም እንደሚያስፈልግም ደመቀ ሲናገሩ ተደምጠዋል ።
ደመቀ፣ እርሳቸው በነበሩበት የአመራር ዘመን ከሁሉም በላይ ትልቅ ቦታ የሚሰጡት ይህ አይነቱ አካሄድ በትውልድ ቅብብሎሽ እና ስልጡን አግባብ መቀጠል ሲችል እንደሆነ ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ደመቀ ፣ ለብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባደረጉት ንግግር ለ31 ዓመት ተኩል በአመራርነት ተከትሎ ከኃላፊነት ለመሰናበት ያቀረቡት ጥያቄ በፓርቲው ተቀባይነት በማግኘቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
ደመቀ፣ ጥያቄያቸው ምላሽ በማግኘቱም በጣም ዕድለኛ ነኝ ሲሉም ተደምጠዋል።
(ንጋት ፕሬስ )
-Advertisement-

